Federalism
የሥልጠናው ርዕስ፡ ፌደራሊዝም
የሥልጠናውአላማ፡ ከዚህ ስልጠና በኃላ ተሳታፊዎች
- የፌደራሊዝምን ፅንሰ ሀሳብን ይረዳሉ፣
- የፌደራሊዝምን ባህርያት ይዘረዝራሉ፣
- ፌደራላዊ ህገ መንግሥትን ባህሪያት ይገነዘባሉ፣
- የፌደራሊዝምን ትርጓሜውን ይረዳሉ፣
- የፌደራሊዝምን አመጣጥና አመሰራረት ይገነዘባሉ፣
- የፌደራሊዝም አስፈላጊነት ይረዳሉ፣
- የፌደሬሽኖች የጋራ ባህሪያት ይዘረዝራሉ፣
- የፌዴራሊዝም ሥርዓት ግንባታ መነሻ ነጥቦች ይዘረዝራሉ፣
- የኢትዮጵያ ፌደራሊዝም መሰረታዊ መርሆዎችና መገለጫዎች ይገነዘባሉ፡፡
የሥልጠናው ይዘት፡ ስለ ፌደራሊዝም ባጠቃላይ እና ኢትዮጲያ ወደ ፌደራሉ ሥርዓት የገባችው ለምንድን ነው የሚሉ ናቸው፡፡
ለስልጠናው የተመደበው ጊዜ፡ 5 ቀናት
የስልጠናው ተሳታፊዎች፡ በፌደራልና በክልል የሲቪል ሰርቪስ መስሪያቤቶች የሚገኙ የከፍተኛ፣መካከለኛ እና ዝቅተኛ ደረጃ አመራሮችና ፕሮፌሽናሎች እንዲሁም የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት ናቸው፡፡
የስልጠናው ዘዴ፡ የስልጠናዉ አሰጣጥ የአሰልጣኞች እና ሰልጣኞችን መማማር እና የጋራ ተሳትፎ መሰረት ያደረገ ሲሆን በቡድን ስራ፣በመልመጃ፣እና ከድርጅቱ እና ከሰልጠኞች የግል ተሞክሮ ጋር የተያያዙ ተዛማጅ ጥናቶችን በማድረግ የሚከወንነዉ፡፡ በእያንዳንዱ የስልጠና መንገድ ስልጠናዉን ከአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ እና የፌደራሊዝም ተግዳሮቶች ጋር ለማገናኘት ከፍተኛ ጥረትይደረጋል፡፡