Basic Concept of Law of Contracts
የስልጠናው ርዕስ፡ መሠረታዊ የውል ሕግ መርሆች
የስልጠናው ዓላማ፡ ከዚህስልጠናበኋላተሳታፊዎች
- የውል ምንነትና አይነቶችን ይረዳሉ፣
- የውል አመሰራረት እንዴት እንደሆነ ይገነዘባሉ፣
- የውሎችን ውጤትና አተረጓጎም ዙሪያ መሰረታዊ ሃሳቦችን ይጨብጣሉ፣
- ውሎችን የማሻሻል አስፈላጊነት ይረዳሉ፣
- ውሎች በማን፣ ለማን፣ እንዴት እናመቼ/የት እንደሚፈፀሙ መተንተን ይችላሉ፣
- የውሎች ውጤት ወደ ሶስተኛ ወገኖች የሚሻገርባቸውን ሁኔታዎች ይዘረዝራሉ እንዲሁም
- ውል ሳይፈጸም ሲቀር የሚኖሩ የመፍትሄ አማራጮችን ያስረዳሉ፡፡
የስልጠናው ይዘት፡ የውል ምንነትና አይነቶች፣ የውል አመሰራረት፣የውሎች ውጤትና አተረጓጎም፣የውል መሻሻል፣ የውል አፈፃፀም፣ውልና ሶስተኛ ወገኖች፣ውልን አለመፈፀም፣ዋስትና፣የግዴታዎች መቅረት እንዲሁም ውልን ማስረዳት ናቸው፡፡
ለስልጠናው የተመደበው ጊዜ፡ 6 ቀናት
የስልጠናው ተሳታፊዎች፡ በፌደራልና በክልል የሲቪል ሰርቪስ መስሪያቤቶች የሚገኙ የከፍተኛ፣መካከለኛ እና ዝቅተኛ ደረጃ አመራሮችና ፕሮፌሽናሎች እንዲሁም የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት ናቸው፡፡
የስልጠናው ዘዴ፡ የስልጠናዉ አሰጣጥ የአሰልጣኞች እና ሰልጣኞችን መማማር እና የጋራ ተሳትፎ መሰረት ያደረገ ሲሆን በቡድን ስራ፣በመልመጃ፣እና ከድርጅቱ እና ከሰልጠኞች የግል ተሞክሮ ጋር የተያያዙ ተዛማጅ ጥናቶችን በማድረግ የሚከወንነዉ፡፡ በእያንዳንዱ የስልጠና መንገድ ስልጠናዉን ከአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ እና መሠረታዊ የውል ሕግ ተግዳሮቶች ጋር ለማገናኘት ከፍተኛ ጥረትይደረጋል፡፡