በኢሲሰዩ ‘‘በሀገረ-መንግስት ግንባታ የምሁራን ሚና” በሚል መሪ ሀሳብ ለ 4 ቀናት በሁለት ዙር ከዩኒቨርስቲዉ የአካዳሚክ ሰራተኞች ፣የአስተዳደርዘርፍ ዳይሬክተሮች እና ከቡድን መሪዎች ጋር ሲካሄድ የነበረዉ ዉይይት ተጠናቋል፡፡
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ‹‹በሀገር ግንባታ የምሁራን ሚና›› በሚል ርዕስ እየተካሄደ ያለው ሀገር አቀፍ ውይይት ታህሳስ 24 ቀን 2015 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ ተጀመረ፡፡
በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከታህሳስ 18 እስከ 21 2015 ዓ.ም ለሁለተኛ ዙር ሲሰጥ የነበረው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በስኬት ተጠናቀቀ፡፡
ፈተናዉ በኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር አማካይነት በዩኒቨርሲቲው ለፈተና የተመደቡ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ከደረሱበት ጊዜ ጀምሮ ተገቢው አቀባበልና የሚያስፈልጓቸው ግብዐቶች በተሟላ መልኩ የቀረበላቸው ሲሆን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የፈተና አሰጣጥ ሂደቱንና ስርዓት በተከተለ ሁኔታ ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብም ባደረገው ኃላፊነትን በብቃት የመወጣት እንቅስቃሴ ፈተናው ያለ ምንም ችግርና እንከን የተሰጠ ሲሆን ተማሪዎቹም በተረጋጋ ሁኔታ ፈተናቸው ለመውሰድ ችለዋል፡፡ በዚህ ዙር ፈተናቸውን እንዲወስዱ የተደረጉት ተማሪዎች በግጭትና በተለያየ ምክንያት በመደበኛው የመጀመሪያ ዙር ሀገር አቀፍ ፈተና ካልተሰጠባቸው አካባቢዎች የመጡ ተማሪዎች መሆናቸውም ታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የስልጠናና ማማከር ዘርፍ ‹‹በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የሴክተር-ተኮርና የብቃት-ተኮር የስልጠናና የማማከር አገልግሎት አሰጣጥ ፤ ፋይዳና የወደፊት አቅጣጫ›› በሚል ርዕስ በቀን ታህሳስ 4 ቀን 2015 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ አውደ-ጥናት አካሄደ፡፡
የአውደ ጥናቱ ዋነኛ ትኩረትም የመንግስት ሰራተኞችን አቅም በመገንባት ረገድ በተቋሙ እስከአሁን ምን ምን ተግባራት እንደተከናወኑ ግንዛቤን በመያዝ በቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት ግልጽ የሆነ አቅጣጫ በማስቀመጥ ለመንቀሳቀስ ያለመ ሲሆን በአውደ ጥናቱ ላይም የተለያ የባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ19ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ 18ኛ ጊዜ የሚከበረዉን የፀረ- ሙስና ቀን ‹‹ሙስናን መታገል በተግባር›› በሚል መሪ ቃል ህዳር 27 ቀን 2015 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲዉ ህዳሴ አዳራሽ በተለያዩ ዝግጅቶች አከበሩ፡፡
We're on Social Networks. Follow us & get in touch.
Please do not hesitate to contact us:
International and Public Relations Directorate:
PoBox: 5648