የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ንጉሥ ታደሰ በዩኒቨርሲቲዉ የሚገኙ ኮሌጆች ፣ትምህርት ክፍሎች እና የተለያዩ የስራ ክፍሎች መጋቢት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጎበኙ፡፡
በሁለተኛ ዙር የተቋም ጉብኝታቸዉ በአካዳሚክ ዘርፍ የተደራጁ የስልጠና ኢንስቲቲዩት፣የፋይናንስ፣ ልማትና ማኔጅመንት ኮሌጅ፣የአመራርና አስተዳደር ኮሌጅ፣የሕግ ትምህርት ቤት፣ ዋና ሬጅስትራር ሲጎበኙ ከየኮሌጆቹ ዲኖች እና ምክትል ዲኖች እንዲሁም የትምህር ክፍል ሃላፊዎች ጋር ተዋዉቀዋል፤ ሀላፊዎቹም ያሉ ነበራዊ ሁኔታዎችን ያብራሩላቸዉ ሲሆን እንደስራ ክፍል የሚያስፈልጉ የግብአት ጥያቄዎችን አቅርበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ንጉሥ ታደሰ በዩኒቨርስቲዉ የተለያዩ የስራ ክፍሎች ጎብኝተዋል፡፡ጉብኝቱም በዋናነት ያተኮረዉ የተጀመሩ ስራዎች በምን ደረጃ ላይ እንዳሉ ፣የተጀመሩ የግንባታ ሂደቶች እና በተቋሙ ያሉ ፋሲሊቲዎች በምን ሂደት ላይ እንዳሉ የመስክ ጉብኝት ማድረግን ያካትታል ፡፡በተጨማሪም የየስራ ክፍሎች አደረጃጀት እና አጠቃላይ አሰራሮች በተመለከተ በየክፍሉ ያሉ የስራ አመራሮች ገለጻ አድርገዉላቸዋል ፡፡
ፕሬዚዳንቱም በጉብኝታቸዉ ላይ እንደተናገሩት በተቋሙ የተፈጠሩ ወደፊትም ለሚፈጠሩ አቅሞች ሙሉ በሙሉ የመጠቀም ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ በማሳሰብ በቀጣይ ለሚከናወኑ የተቋሙ ስትራቴጅካዊ ተግባራት በየዘረፎቹ ላሉ የስራ ክፍሎች ለሚሰሯቸው ማናቸውም ሥራዎች በዩኒቨርሲቲው በኩል የሚጠበቁ ድጋፎች እንደሚደረጉ እና እንደ አመራርም ቁርጠኝነት መኖሩን አረጋግጠዋል፡፡
We're on Social Networks. Follow us & get in touch.
Please do not hesitate to contact us:
International and Public Relations Directorate:
PoBox: 5648