የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ መጋቢት 28 ቀን 2015 ዓ.ም የመስክ ምልከታና ውይይት አካሄደ ፡፡ የመስክ ምልከታው ዓላማም በዩኒቨርሲቲው ያለው የመማር ማስተማር ስራ ያለበትን ደረጃ ማረጋገጥ ሲሆን በምልከታ ወቅትም ከዩኒቨርሲቲው የተለያዩ የስራ ክፍሎች፣ ከመምህራንና የተማሪ ተወካዮች ጋር እንዲሁም ከዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራሮች ጋር የተናጠል ውይይቶችን አድርጓል፡፡