Ethiopian Civil Service University (ECSU) College of Leadership and Governance, Institute of African Governance and Development held a Conference on Migratory Trends in the Horn of Africa on October 23, 2024 at ECSU.
የኢሲሰዩ ካውንስል ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ/ም ባካሄደው የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድና የ1ኛ ሩብ አመት የሪፎርም የስራዎች አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ፣ የከፍተኛ ትምህረት ተቋማት፣ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን እውቅና ለማግኘት፣ ከሙጁላር የትምህርት አሰጣጥ ስርዓት ወጥተው፣ በብቃት ተኮር የትምህርት አሰጣጥ ስርዓት (Outcome based education system) ማስተማር እንዳለባቸው ለካውንስሉ አባላት ማብራሪያ ተሰጠ፡፡
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የመደበኛና የሪፎርም ስራዎች አፈጻጸም ግምገማ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም በሕዳሴ አዳራሽ አካሄደ፡፡ በግምገማ መድረኩም የ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ ዕቅድ ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖረት ላይ ካውንስሉ በዝርዝር ተወያይቷል፡፡
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባቸውን 25 የንግድ ሱቆች በዩኒቨርሲቲው ለሚሰሩና በየካ ክፍለ ከተማ በወረዳ 09 ለሚገኙ በአነስተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጳጉሜ 1 ቀን 2016 ዓ.ም በዕጣ አስተላለፈ፡፡
በርክክብ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ ለተጠቃሚዎች ባስተላለፉት መልዕክት ተጠቃሚዎቹ በተለይ አነስተኛ ገቢ ያላቸዉ ተጨማሪ ገቢ ማስገኛ እንደሚሆን በመግለጽ ዩኒቨርስቲዉ እንዲህ አይነት ድጋፍ ሲያደርግ ለሁለተኛ ግዜ መሆኑን በመግለጽ ወደፊትም በተቻለ መጠን ማህበራዊ ግዴታዉን እንደሚወጣ ገልጸዋል፡፡ የተዘጋጀው ውል በጥንቃቄ በመረዳት የተቀመጠውን ህግና ደንብ አክብረው፣ የሚጠበቅባቸውን ግዴታ በአግባቡ በመወጣት ፤ በተለያዩ ነገር ግን ገበያ ተኮር ባደረጉ የስራ መስኮች ላይ ተሰማርተው እንዲሰሩ አሳስበዋል፡፡የዚህ ዕድል ተጠቃሚ ለመሆን በመቻላቸው እንኳን ደስ አላችሁ በማለት መልካም የሥራ ስኬትን ተመኝተዋል፡፡
We're on Social Networks. Follow us & get in touch.
Please do not hesitate to contact us:
International and Public Relations Directorate:
PoBox: 5648