በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረውን የጸረ ሙስና ቀን ‘‘ሙስና ጠላታችን ነው ፤በጋራ እንታገለው’’ በሚል መሪ ቃል የዩኒቨርስቲዉ ሰራተኞች እና አመራሮች በተገኙበት ህዳር 26 ቀን 2016 ዓ/ም በፓናል ውይይት እና በተቋሙ በስጋት አስተዳደር ላይ የተካሄደ የጥናት ግኝት በማቅረብ ተከብሯል፡፡
የውይይቱን መድረክ የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ በአስተላለፉት መልዕክት ‘‘ ሙስና ግዑዝ ነገር አይደለም ፤ሀብት በአግባቡ ለታለመለት ጉዳይ አለማዋል ማለት ነዉ ፡፡በዚህም አመራሮች የመወሰን ስልጣን ያለን የመንግስት ሀብት በአግባቡ እየተጠቀምን ነዉ ወይ የሚለዉን መጠየቅ ፣ተቋማችንን እያየን በመገምገም አቅጣጫ እያስቀመጥን የጋራ ግንዛቤ በመያዝ የጸረ ሙስና ትግል አካል ሆነን እነደ ዜጋ ድርሻችንን መወጣት አለብን ብለዋል ፡፡’’