የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል የ2015 ዓ.ም የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማውን የዩኒቨርሲቲዉ የካዉንስል አባላት በተገኙበት ጥር 5 ቀን 2015 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ አካሄደ፡፡
በግምገማዉ መክፈቻ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ ለካውስሉ አባላት ባደረጉት ንግግር በየሩብ ዓመቱ ጊዜውን ጠብቆ ሲካሄድ የነበረው የካውንስል ስብሰባ እና የዩኒቨርሲቲው የስራ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በጥቅምት ወር በዩኒቨርሲቲው በተሰጠው የአስራ ሁለተኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ምክንያት ባለመካሄዱ በዚህ ስብሰባ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የሥራ ክንውንን ጨምሮ አጠቃላይ የስድስት ወር የአፈጻጸም ሪፖረትት ቀርቦ ግምገማ እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡