የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሀገሪቱ ከሚገኙት የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች ጋር መመደቡን ተከትሎ በተዘጋጀው አዲስ የአደረጃጀት መዋቅር መሰረት በዩኒቨርሲቲው የስልጠና ኢንስቲትዩት ስር ለሚገኙ የስራ መደቦች ለተመደቡ አዳዲስ አመራሮች በመጋቢት 11ቀን 2015 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ ትውውቅ መርሃ ግብር አዘጋጀ፡፡
በትውውቁ መርሀ ግብሩ ላይም የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ በአዳዲስ የስራ መደቦቹ ላይ ለተመደቡት አመራሮች ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግርና በሰጡት የስራ መመሪያ ላይ በአዲሱ አደረጃጀት መሰረት የስልጠና ኢንስቲትዩቱ በዩኒቨርሲቲው ተልዕኮ መሰረት ለፌደራል ተቋማት እና ለአዲስ አበባ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ ተቋማት አጫጭር ስልጠናዎችን በመስጠት አቅማቸው የመገንብት ኃላፊነት አንደሚኖረው ገልጸዋል፡፡