የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢሲሰዩ) ከኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር ጋር በተፈራረመው የዕቅድ አፈጻጸም ውል መለኪያ በሆኑት የቁልፍ ውጤት አመላካቾች (Key Performance Indicators/ KPI) ዙርያ ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ ገለጻ እና ማብራሪያ ተሰጠ፡፡ ገለጻውን የሰጡት የኢሲሰዩ ፕሬዚደንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ ሲሆኑ በመርሀ- ግብሩ ላይም የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚደንቶች፣ ዲኖች ፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች እና ሥራ አስፈጻሚዎች ተሳትፈዋል፡፡