የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ የኮሌጅ ዲኖች፣ ምክትል ዲኖችና የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች ዩኒቨርሲቲው ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን እያደረገ ባለው የሽግግር ወቅት ተግባራት እና ዩኒቨርሲቲው እስካሁን ባደረጋቸው እንቅስቃሴዎች ላይ ጥር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ በተደረገው ውይይት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ መሆን ለዩኒቨርሲቲዎች ትልቅ ዕድል እንጂ እንደ ስጋት ሊወሰድ እንደማይገባው ገልጸዋል፡፡
በውይይቱ መክፈቻ ላይ ፕ/ር ፍቅሬ በሰጡት ማብራሪያ መድረኩ ቀደም ሲል የተጀመረው የለውጥ ስራዎች ላይ ያለውን የሀሳብ ግልጽነት የሚያስፈልጋቸው ሀሳቦች እንዲሁም በቀጣይነት የሚሰሩ ስራዎች ላይ ግልጽነት ለመፍጠር የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን ጠቅሰው እንደ ሀገር የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች በቀጣዩ ሶስት ዓመታት ውስጥ ወደ ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲነት እንዲገቡ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ የሽግግር እቅድ አዘጋጅተን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል፡፡