የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች በመደበኛ፣በክረምት፣ በኤክስቴንሽን መረሃ-ግብር ሲያስተምራቸው የቆዩ 180 በመጀመሪያ ዲግሪ 2186 በሁለተኛ ዲግሪ እንዲሁም 11 በፒኤችዲ ዲግሪ በድመሩ 2377 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2015ዓ.ም በዩኒቨርስቲዉ ዋና ግቢ አስመርቋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ ፣ የዩኒቨርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ አባል እንዲሁም የዕለቱ የክብር እንግዳ የሆኑት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስተር ዲኤታ ጨምሮ የሴኔት አባላት፣ የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል፡፡