የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢሲሰዩ) በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን 2312 ተማሪዎች በመጀመሪያ፣ ሁለተኛና በፒኤች ዲ በአደዋ ድል መታሰቢያ ፓን አፍሪካ የመሰብሰቢየ አዳራሽ ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም በድምቀት አስመረቀ፡፡ ከመደበኛ ፕሮግራሙ ባሻገርም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር ባለው ትብብር በልዩ ፕሮግራም ሲያሰለጥናቸው የቆዩ 24 ዕጩ ዲፐሎማቶችንም በከፍተና ዲፕሎማ ሰርቲፊኬት አስመርቋል፡፡