2017 ዓ.ም በሀገርአቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው የ12ኛ ክፍል መልቀቅያ ፈተና ለመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በ ዩኒቨርሲቲዉ ዋና ግቢ ገለጻ ተሰጠ፡፡
በገለጻዉ ላይ የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዚዳንት ፣ምክትል ፕሬዚዳንት ፣የፈተና አስተባሪዎች፣ጣቢያ ኃላፊዎች እና የፈተና ኮሚቴ ግብረ ኃይል በተገኙበት ለተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናው በሰላማዊና በተገቢው ሁኔታ እንዲጠናቀቅ በፈተና ወቅት ከተፈታኝ የሚጠበቁ ግዴታዎች እና መብቶች እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው በፈተና ቆይታቸው ሊፈጽሟቸው የሚገቡ ህገ-ደንቦች ዙርያ ዝርዝር ገለጻና ማብራሪያ ተሰጥቷል ፡፡