የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ንጉሥ ታደሰ በዩኒቨርሲቲዉ የሚገኙ ኮሌጆች ፣ትምህርት ክፍሎች እና የተለያዩ የስራ ክፍሎች መጋቢት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጎበኙ፡፡
በሁለተኛ ዙር የተቋም ጉብኝታቸዉ በአካዳሚክ ዘርፍ የተደራጁ የስልጠና ኢንስቲቲዩት፣የፋይናንስ፣ ልማትና ማኔጅመንት ኮሌጅ፣የአመራርና አስተዳደር ኮሌጅ፣የሕግ ትምህርት ቤት፣ ዋና ሬጅስትራር ሲጎበኙ ከየኮሌጆቹ ዲኖች እና ምክትል ዲኖች እንዲሁም የትምህር ክፍል ሃላፊዎች ጋር ተዋዉቀዋል፤ ሀላፊዎቹም ያሉ ነበራዊ ሁኔታዎችን ያብራሩላቸዉ ሲሆን እንደስራ ክፍል የሚያስፈልጉ የግብአት ጥያቄዎችን አቅርበዋል፡፡