የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዞችን የአገር ውስጥ እና የውጭ አገር ገበያ ትስስር ውጤታማነትና ዘላቂነት ለማረጋገጥና ፀጋን ለመለየት የሚያስችል ጥናት የማማከር ውል ስምምነት ሰነድ ከኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ጋር ተፈራርሟል።
ኢንተርፕራይዞች የሚገጥማቸውን ችግር በጥናት በመለየት በጥናቱ ግኝት መሰረት አሰራርን በማሻሻል እና ለፖሊሲ ግብአት ከመጠቀም ባለፈ የመክሰም ምጣኔ በመቀነስ እና ዘላቂ የገበያ ትስስር በመፍጠር ሂደት የመፍትሄ ሃሳብ ለማቅረብ እንደሚያግዝ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዘዳንት ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ ዩኒቨርሲቲው ከዚህ ቀደም ከከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ ተቋማት ጋር የተለያዩ ጥናትና ምርምር ስራዎችን ማካሄዱን በማስታወስ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ጥናቱን ሰርቶ ለማስረከብ ከቢሮው ጋር በቅርበት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢሲሰዩ) ከኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር ጋር በተፈራረመው የዕቅድ አፈጻጸም ውል መለኪያ በሆኑት የቁልፍ ውጤት አመላካቾች (Key Performance Indicators/ KPI) ዙርያ ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ ገለጻ እና ማብራሪያ ተሰጠ፡፡ ገለጻውን የሰጡት የኢሲሰዩ ፕሬዚደንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ ሲሆኑ በመርሀ- ግብሩ ላይም የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚደንቶች፣ ዲኖች ፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች እና ሥራ አስፈጻሚዎች ተሳትፈዋል፡፡
We're on Social Networks. Follow us & get in touch.
Please do not hesitate to contact us:
International and Public Relations Directorate:
PoBox: 5648