የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር በክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የተመራና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተ ቡድን ከኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮችና ከከተማ ልማትና ምህንድስና ኮሌጅ የተለያዩ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አደረጉ፡፡ ሰኔ 11 ቀን 2016 ዓ.ም ክብርት ሚኒስትሯ በዩኒቨርሲቲው ባደረጉት ጉብኝት ወቅት በተደረገው በዚሁ ውይይት ላይም በዩኒቨርሲቲውና በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መካከል ያለውን ነባር ትብብር የበለጠ ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በስፋት ተወያይተዋል፡፡