የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የስልጠናና ማማከር ዘርፍ ‹‹በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የሴክተር-ተኮርና የብቃት-ተኮር የስልጠናና የማማከር አገልግሎት አሰጣጥ ፤ ፋይዳና የወደፊት አቅጣጫ›› በሚል ርዕስ በቀን ታህሳስ 4 ቀን 2015 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ አውደ-ጥናት አካሄደ፡፡
የአውደ ጥናቱ ዋነኛ ትኩረትም የመንግስት ሰራተኞችን አቅም በመገንባት ረገድ በተቋሙ እስከአሁን ምን ምን ተግባራት እንደተከናወኑ ግንዛቤን በመያዝ በቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት ግልጽ የሆነ አቅጣጫ በማስቀመጥ ለመንቀሳቀስ ያለመ ሲሆን በአውደ ጥናቱ ላይም የተለያ የባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡